በምሥራቅ አፍሪካ በጎርፍ መጥለቅለቅና፣ በመሬት መንሸራተት 3.6 ሚሊዮን የሚገመት ሕዝብ ለአደጋ መጋለጡ ተገለጸ።
- #ናይ ሓሶት ዜና የብቅዕ – ክፋልን 2 ብትግርኛ
- #ሐስት ዜና ይብቃ – በCNN ዋና መሥሪያ ቤት
- 5 ፓርቲዎች ታሪካዊ የጋራ መግለጫ!
- አቶ ላዕክ ማለደ በኢትዮጵያ ሁኔታ ላይ በቅርቡ በአማራ ቲቪ
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶክተር) የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ ልዩ ስብሰባ
- የ72 ሰዓት ጊዜው ገደብ ሲያበቃ የአፍሪካ ህብረት ልዑካን ወደ ኢትዮጵያ አመሩ
- ፋኦ በኢትዮጵያ የተከሰተውን የአንበጣ ወረራ፤ ኮሺድ-19 ና የጎርፍ መጥለቅለቅ በጣም አሳሳቢነቱን ይፋ አደረገ
- የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ 2020 ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ ተብሎ ተሸለመ።
- ዶናልድ ትራምፕ ግብፅ “ያንን ግድብ ታፈነዳለች፤ አንድ ነገር ማድረግ አለባት “ማለታቸው ከአንድ ፕሬዚዳንት የማይጠበቅ ጠብ አጫሪነት ነው ተባለ
- በምሥራቅ አፍሪካ በጎርፍ መጥለቅለቅና፣ በመሬት መንሸራተት 3.6 ሚሊዮን የሚገመት ሕዝብ ለአደጋ መጋለጡ ተገለጸ።

ካለፈው ሰኔ ወር ጀምሮ በመላው ምስራቅ አፍሪካ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በተቀሰቀሰው የጎርፍ መጥለቅለቅ እና የመሬት ናዳ ቢያንስ 3.6 ሚሊዮን ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ አገልግሎት ድርጅት ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል ፡፡የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት (OCHA) “በኬንያ እና በኡጋንዳ የበርካታ ሐይቆች የውሃ መጠን የጨመረ ሲሆን ይህም በሺዎች የሚቆጠሩ ሕዝቦችን ለአደጋ አጋልጧል፡፡
በደቡብ ሱዳን ከሰኔ ወር ጀምሮ 856,000 ያህል ሰዎች ለጎርፍ ተጋልጠዋል ፣ የተፈናቀሉት በግምት 400,000 እንድሚሆኑ በሪፖርቱ ተካቷል፡፡ በክልሉ ውስጥ ብአሁኑ ወቅት በሕዝቡ ላይ ተጋርጠው ያሉት ግጭቶች፣ ሁከቶች ፣ የበረሃ አንበጦች እና COVID-19 ላይ ይኸ ተጨምሮ ሕዝቡ ለከፍተኛ ችግር ተጋልጧል ፣
ሪፖርቱ እንዳመለከተው በኢትዮጵያ 1.1 ሚሊዮን ያህል ሰዎች በጎርፍ የተጠቁ ሲሆን ከ313,000 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በኬንያ ከጥቅምት እስከ ዲሴምበር 2019 አካባቢን ያጥለቀለቀው ከፍተኛ የወቅቱን ዝናብ ተከትሎ በርካታ የስምጥ ሸለቆ ሐይቆች በተለይም ባሪንጎ እና ናይቫሻ የውሃ ደረጃዎች “በታሪክ ከፍተኛ ናቸው” ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታውቋል ፡
በተጨማሪም አካባቢው በ2020 በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ከቀዬአቸው በመፈናቀላቸው በኑሮ ፣ በትምህርት ቤቶችና በጤና ተቋማት ላይ ተጽዕኖ እንዳሳድር ሪፖርቱ ጠቋሷል።